
Experience
Junior Level(1-3 years)
Salary
Not specified
Posted
about 5 hours ago
Deadline
in about 1 month
Job Description
ድርጅታችን ኤ እና ኤም ኢንጅነሪንግ ቀልጣፋ፣ ንቁ እና ከፍተኛ የማደራጀት ብቃት ያለው/ላት የጉዳይ አስፈፃሚ ሙያ ያለው ሰራተኛ ይፈልጋል። ይህ የሥራ መደብ በቢሮ ውስጥ የደንበኞችን መረጃ እና ለድርጅታችን ጉዳዮች የማስተዳደር፣ እንዲሁም በውጭ ያሉ የድርጅቱን እና የመንግሥት ጉዳዮችን (ጉዳይ አስፈጻሚነትን) አጣጥሞ የመስራት ኃላፊነትን ያካትታል። በመሆኑም ጉዳይ አስፈፃሚ የሥራ ቦታ ብቁ አመልካችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
- በድርጅቱና በተለያዩ የመንግሥት/የግል ተቋማት (እንደ ገቢዎች፣ ንግድ ሚኒስቴር፣ ባንኮች፣ ወዘተ) መካከል ያሉ ጉዳዮችን መከታተልና ማስፈጸም።
- የንግድ ፈቃድ ማደስ፣ የግብርና ታክስ ፋይሎችን ማስተካከል እና የውሃ/መብራት/ስልክ ክፍያዎችን መፈጸም።
- የባንክ ሥራዎችን (ገንዘብ ማስገባት፣ ሰነዶችን ማድረስና መቀበል) ማከናወን።
Requirements
የት/ደረጃ
12ኛ ክፍል ያጠናቀቀ/ች፣ ወይም በማኔጅመንት፣ በሕግ፣ በአስተዳደር ወይም በተዛማጅ መስኮች ዲፕሎማ/ሰርተፊኬት ያለው/ላት።
የሥራ ልምድ፡
ከ 2 እስከ 4 ዓመት በጉዳይ አስፈጻሚነት የሠራ/ች ይመረጣል።
- ክህሎት፡
ከፍተኛ ንቁነት መልካም የኮሚዩኒኬሽን ችሎታ፣ ከተለያዩ ተቋማት ጋር የመደራደር/ የማስፈጸም ብቃት።
- ታማኝነት፡ ሙሉ በሙሉ የታመነ እና የጠራ ስም ያለው (ኃላፊነት ስላለው) ፤
- ቅልጥፍና፡ ያለምንም ማስታወሻ እና ማሳሰቢያ ትእዛዞችን በፍጥነት እና በሰዓቱ የመፈጸም አቅም፤
- የቴክኖሎጂ እውቀት፡ በኤክሴል (Excel፣ በሞባይል ባንኪንግ (ቴሌብር / CBE Birr) እና በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ በቂ እውቀት ያለው፤
- ግንኙነት፡ በአማርኛ ቋንቋ ጥሩ የጽሁፍ እና የንግግር ችሎታ ያለው (መሰረታዊ የእንግሊዝኛ እውቀት ያለው ይመረጣል) ፤
- ተጨማሪ ባህሪያት፡ ሰዓት አክባሪ፣ ራሱን በአግባቡ የሚጠብቅ እና ለደንበኞች ከፍተኛ አክብሮት ያለው።
Required Skills
Level
Junior Level(1-3 years)
Location
Addis Ababa