
Experience
Entry Level
Salary
ETB 13K - 13K
Posted
about 6 hours ago
Deadline
in 4 days
Job Description
የስራ መስፈርቶች
የትምህርት ደረጃ፡ በነርሲንግ በደረጃ 4 የተመረቀ/ቀች
የስራ ልምድ፡ 0 ዓመት
ብዛት፡ 1
ደመወዝ ፡ 12566
ደረጃ፡ X
የመ/መ/ቁጥር፡ 8.32/ወቂዩ-2185
የቅጥር ሁኔታ፡ ኮንትራት
የስራ ቦታ፡ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለቡኢ ልዩ አዳር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
ዋና ዋና ኃላፊነቶች
የታካሚዎችን የጤና ሁኔታ መከታተልና መመዝገብ
በሐኪም ትዕዛዝ መሠረት መድኃኒትና ሕክምና መስጠት
የታካሚዎችን የነርሲንግ እንክብካቤ መስጠት
የታካሚዎችን ቁስል መንከባከብና የሕክምና ሂደት መከታተል
የታካሚ መረጃና የሕክምና መዝገቦችን በአግባቡ መያዝ
ለታካሚዎችና ለቤተሰቦቻቸው የጤና ትምህርትና ምክር መስጠት
አስቸኳይ የጤና ሁኔታዎችን መለየትና ተገቢውን እርምጃ መውሰድ
የማመልከቻ መመሪያ
አመልካቾች የትምህርት እና የስራ ልምድ ማስረጃ በእንድ ፒዲኤፍ በማድረግ በኢሜል አድራሻችን hr@wku.edu.et ወይም የስራ መደቡን በመጥቀስ ማመልከቻ፣ የትምህርት ማስረጃ ኦርጅናል ከማይመለስ ፎቶኮፒ ጋር በመያዝ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የብቃትና ሰዉ ሀብት አስ/ሥራ አሥፈፃሚ ቢሮ አዲሱ ህንፃ ግራውንድ ቢሮ ቁጥር G- 031 ወይም ቡታጅራ አካባቢ ያላችሁ ተመዝጋቢዎች በቡታጅራ ካምፓስ የብቃትና ሠው ሃብት አስተዳደር ቢሮ በአካል በመገኘት ማመልክት ይችላሉ፡፡
ማስታወሻ፡ አመልካቾች የCOC ምዘና ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ በላይ የትምህርት እና የስራ ልምድ ማስረጃ ያላቸው አመልካቾች ማመልከት የሚችሉ ሲሆን ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የዲግሪ የትምህርት ማስረጃ የሚያቀርቡ አመልካቾች የመውጫ ፈተና ያለፉበትን መረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በተጨማሪም አመልካቾች የተደራጀ እና የተሟላ የስራ ልምድ አያይዞ ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን ለሚያቀርቡት የትምህርት ማስረጃ ህጋዊነት ላይ ሙሉ በሙሉ ሃላፊነት ይኖርባቸዋል፡፡ ከግል ተቋማት የሚቀርቡ የስራ ልምድ ማስረጃዎች የስራ ግብር የተከፈለባቸው መሆን ይኖርባቸዋል። ተመዝጋቢዎች ለጽሁፍ ፈተና የተመለመሉ ተወዳዳሪዎች የፈተና ቀናት በውስጥ ማስታወቂያና በተቋሙ ድረ-ገጽ ቴሌግራምና በፌስቡክ ገጽ ይገለፃል ፡፡
Requirements
Required Skills
Level
Entry Level
Location
Wolkite